#Ethiopia | በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተካሄደው ደማቅ የድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ውድድር ጆኒ ተጋጣሚውን ሴዶን በመጀመሪያው ዙር በፍጥነት በማሸነፍ የክብር ቀበቶውን ተረክቧል።
በተደራጀ የመድረክ ዝግጅት፣ በታዳሚዎች ደማቅ ተሳትፎና በስፖርተኞች ብርቱ ፉክክር የተካሄደው “አድዋ ፋይት ናይት 2” የሀገራችንን የማርሻል አርት ውድድር ደረጃ ከፍ ባደረገ መልኩ ተጠናቋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ ከዋናው የMMA ፍልሚያ በተጨማሪ የቦክስ እና የሞይታይ (Muay Thai) ውድድሮች ተካሂደው የተመልካቹን ቀልብስበዋል።
በዕለቱ ታዋቂ አርቲስቶች፣ የቲክቶክ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችና በርካታ የስፖርት አፍቃሪዎች በተገኙበት ጆኒ የበላይነቱን በማስመስከር የደማቁ ምሽት አሸናፊ መሆን ችሏል።
#MMA #AdwaFightNight #AdwaFightNight2 #Johnny #EthiopiaMMA #MartialArts


Source: GetuTemesgen








No comments yet.