የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት በአሳሳቢ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ‹‹ዎል ስትሪት ጆርናል›› የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ዘ…

- Advertisement -
Sidebar AD

የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት በአሳሳቢ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ‹‹ዎል ስትሪት ጆርናል›› የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ዘገበ።
በመካከለኛው ምስራቅ ከኢራን ጋር ያለው ግጭት በአውሮፓ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር መሣሪያዎች ክምችት ክፉኛ እየጎዳው መሆኑ ተገልጿል።
በተለይም የ‹ፓክ-3 ፓትሪዮት› ሚሳኤል መከላከያዎች እና የረዥም ርቀት ሚሳኤሎች ክምችት ከወትሮው በበለጠ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተመላክቷል።
በዚህም ግጭት እስካሁን፦ 1 ሺህ 7 መቶ የፓትሪዮት ሚሳኤል መከላከያዎች፣ 2 መቶ የታድ መከላከያዎች፣ እና 150 የባህር ኃይል ስታንዳርድ ሚሳኤሎች አገልግሎት ላይ ውለዋል።
ይህንኑ እጥረት ለማቃለል ሲባልም፤ በርካታ የታድ ስርዓቶች እና ድሮን ተከላካይ መሣሪያዎች ከአውሮፓ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ተዛውረዋል።
ይህ የመሣሪያዎች እጥረት አሁን በጦርነት እቅድ ዝግጅት ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ፣ የአሜሪካ አውሮፓ እዝ የተግባር እቅዶቹን ማስተካከሉ ተሰምቷል።
ነጩ ቤተ መንግስት እና ፔንታጎን ግን “እጥረት አለ” የሚለውን ዘገባ በመቃወም፣ ያለው ክምችት ለስትራቴጂካዊ አላማዎች በቂ እንደሆነ አስምረው ተናግረዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: