“መንግሥት ከተጠያቂነት ሊያመልጥ አይችልም!” — አብን
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በንጹኃን ላይ የተፈጸሙትን ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ የእምነት ተቋማት ውድመትና እገታዎችን በጽኑ ኮንኗል።
ንቅናቄው ባወጣው መግለጫ፣ መንግሥት የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅ ኃላፊነቱን አልተወጣም ሲል ከሷል። ጥቃቱን በታጣቂዎች ላይ ብቻ በማሳበብ መንግሥት ከተጠያቂነት ነፃ ሊሆን እንደማይችል የገለጸው አብን፣ በጸጥታ መዋቅሩ ላይ ላለው ውድቀት የባለሥልጣናት ተጠያቂነት ሊረጋገጥ እንደሚገባ አሳስቧል።
አብን አክሎም፣ የዜጎች የመኖር መብት ባልተከበረበት ሁኔታ ስለ አገራዊ ብልፅግና ማውራት እውነታውን መካድ ነው ብሏል። ችግሩን ዘላቂ በሆነ መንገድ ለመፍታት የፌደራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት የተቀናጀ እርምጃ እንዲወስዱ፣ ገለልተኛ አካላት የሚሳተፉበት የምርመራ ሥርዓት እንዲዘረጋና ተፈናቃዮች በአስቸኳይ ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርቧል።
@Seledadotio
@Seledadotio
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በንጹኃን ላይ የተፈጸሙትን ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ የእምነት ተቋማት ውድመትና እገታዎችን በጽኑ ኮንኗል።
ንቅናቄው ባወጣው መግለጫ፣ መንግሥት የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅ ኃላፊነቱን አልተወጣም ሲል ከሷል። ጥቃቱን በታጣቂዎች ላይ ብቻ በማሳበብ መንግሥት ከተጠያቂነት ነፃ ሊሆን እንደማይችል የገለጸው አብን፣ በጸጥታ መዋቅሩ ላይ ላለው ውድቀት የባለሥልጣናት ተጠያቂነት ሊረጋገጥ እንደሚገባ አሳስቧል።
አብን አክሎም፣ የዜጎች የመኖር መብት ባልተከበረበት ሁኔታ ስለ አገራዊ ብልፅግና ማውራት እውነታውን መካድ ነው ብሏል። ችግሩን ዘላቂ በሆነ መንገድ ለመፍታት የፌደራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት የተቀናጀ እርምጃ እንዲወስዱ፣ ገለልተኛ አካላት የሚሳተፉበት የምርመራ ሥርዓት እንዲዘረጋና ተፈናቃዮች በአስቸኳይ ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርቧል።
@Seledadotio
@Seledadotio
Related Posts
- Advertisement -








No comments yet.