የነጭ ጋውኑ ጀግኖች

- Advertisement -
Sidebar AD

የቅዱስ ጳውሎስ 2018 ተመራቂዎች የላቀ ውጤት

#Ethiopia | ​የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የሕክምና ተመራቂዎች በዛሬው ዕለት ደማቅ የምረቃ ስነ-ስርዓት አካሂደዋል።

በምረቃው ላይ እጅግ አስደናቂ ውጤት ያስመዘገቡ ወጣት ሐኪሞች የኮሌጁና የሀገሪቱ ኩራት ሆነዋል።

​ የዘንድሮው ኮከብ ተመራቂዎች

​የአንደኛ ደረጃ ባለቤት፦ ዶ/ር ይክበር ቴዎድሮስ — 3.95 በማምጣት በ”እጅግ በጣም ከፍተኛ ማዕረግ” (Great Distinction) ትምህርቱን አጠናቋል።

​የሁለተኛ ደረጃ ባለቤት፦ ዶ/ር ኢማን አብዱራህማን — 3.94 በማምጣት የላቀ ውጤት አስመዝግባለች።

​የሦስተኛ ደረጃ ባለቤት፦ ዶ/ር ሙሉዓለም አንተነህ — 3.87 በማምጣት በከፍተኛ ማዕረግ ተመርቃለች።

​ዛሬ በለንደን ማራቶንና በሸገር ደርቢ ድሎች ስንኩራራ ብንውልም፣ እንደነዚህ ያሉ ወጣት ሐኪሞች ለሀገራቸው ጤና ዘርፍ የላቀ ውጤት ይዘው ሲወጡ ማየት የሁሉንም ድል በረከት ያደርገዋል። 3.95 እና 3.94 ማምጣት ትልቅ ጥረትና ትጋትን ይጠይቃል። እነዚህ ወጣቶች የነገዋን ኢትዮጵያ በዕውቀት የሚፈውሱ ጀግኖች ናቸው። እንኳን ደስ ያላችሁ!”

​ዕውቀት ለሀገር ፈውስ ነው!

​#getu #StPaulsGraduation #MedicalDoctors #EthiopiaGraduation2018 #DoctorYikberTheodros #ExcellenceInMedicine #MedicalStudentLife #ኢትዮጵያ #ቅዱስጳውሎስ #ሕክምና #ምረቃ #ጀግኖች #ጌጡተመስገን #GetuTemesgen


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: