እነ ጌታቸው ረዳ ትግራይን ለመቆጣጠር ምክር ቤት መሠረቱ !!በህወሓት ጫና ከትግራይ የሸሹ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ክልሉን መልሶ ለመ…

- Advertisement -
Sidebar AD
እነ ጌታቸው ረዳ ትግራይን ለመቆጣጠር ምክር ቤት መሠረቱ !!
በህወሓት ጫና ከትግራይ የሸሹ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ክልሉን መልሶ ለመቆጣጠር ያስችለናል ያሉትን ምክር ቤት ዛሬ በአዲስ አበባ መሥርተዋል።
እንደ ጌታቸው ረዳ እና ጀነራል ጻድቃን ገብረተንሳይ ያሉ የህወሓት ተቃዋሚዎች የመሰረቱት፣ “የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት” የተሰኘ ተቋም ነው።  ምክር ቤቱ የተመሰረተው በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሰውን ሓራ መሬት ወይይ የትግራይ ለውጥ ኃይል ታጢቂ ቡድን አዛዥ ጀኔራሎች አቅፎ መሆኑ ታውቋል።
በአዲስ አበባ ከተማ መመስረቱ የተነገረለት የለውጥ ኃይሎች ምክር ቤት፣ ህወሓት አስወግዶ ትግራይን ለመቆጣጠር የሚሠራ ነው ተብሏል።
በህወሓት ግፊት ከትግራይ የወጡት የፖለቲካ ኃይሎች እና አፋር ክልል የመሸገው ታጣቂ ቡድን በቀጣይ ስለሚኖራቸው የጋራ ትግል ሲመክሩ መሰንበቻውን ተገልጿል።
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2