#Ethiopia | የፊፋው ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ የኢራን ብሔራዊ ቡድን በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ እንደሚሳተፍ በይፋ አረጋግጠዋል።
ፕሬዝዳንቱ በሰጡት ማብራሪያ፣ የኢራን ብሔራዊ ቡድን በውድድሩ ላይ ተገኝቶ ሀገሩንና ህዝቡን መወከል እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ወቅታዊ ውጥረት አስመልክተውም፣ ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት ነገሮች ሰላማዊ እንደሚሆኑና ሁኔታዎች እንደሚረጋጉ ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።
“ኢራን መካፈሏ እርግጥ ነው” ያሉት ኢንፋንቲኖ፣ ስፖርት የህዝቦች መገናኛ ድልድይ መሆኑን በድጋሚ አስመስክረዋል።
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#FIFA2026 #IranNationalTeam #GianniInfantino #WorldCup #FootballNews #LeadThePlot #SportsDiplomacy
Source: GetuTemesgen









No comments yet.