#FastMereja I የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በሊባኖስ ለተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት እውቅና በመስጠት፣ ስልታዊ ጠቀሜታ ያለው የሆርሙዝ ወሽመጥ ለሁሉም የንግድ መርከቦች “ሙሉ በሙሉ ክፍት” መሆኑን ዛሬ አርብ አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው በቴህራን ላይ የተጣለው የባህር ኃይል እገዳ አሁንም “በሙሉ ኃይሉ” እንደሚቀጥል በመግለጽ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
ሚኒስትር አራቅቺ በኤክስ (X) ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መረጃ፣ መርከቦች በኢራን የወደብና የባህር ኃይል ድርጅት በኩል ቀደም ሲል በወጣው የተቀናጀ መስመር መጓዝ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ይህ ማስታወቂያ መውጣቱን ተከትሎም በዓለም አቀፍ ገበያ የነዳጅ ዋጋ እስከ 9 በመቶ የሚደርስ ከፍተኛ ቅናሽ አሳይቷል።
በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢራንን ውሳኔ “እናመሰግናለን” በማለት በበጎ ቢቀበሉትም፣ ከኢራን ጋር አዲስና የተሻለ ስምምነት ላይ እስካልተደረሰ ድረስ ግን የአሜሪካ የባህር ኃይል እገዳ እንደማይነሳ በድጋሚ አረጋግጠዋል። በሊባኖስ በኩል ያለው የ10 ቀናት የተኩስ አቁም ለጊዜው ተስፋ የሰጠ ቢሆንም፣ በዋሽንግተን እና በቴህራን መካከል ያለው ፍጥጫ ግን አሁንም እንደቀጠለ ነው።
Source: FastMereja









No comments yet.