ባየር ሙኒክ ሻምፒዮን ሆነ

- Advertisement -
Sidebar AD

📌የቡንደስሊጋው ዘውድ ወደ አሊያንዝ አሬና ተመልሷል!

#Ethiopia | ​የጀርመን እግር ኳስ የበላይነት በድጋሚ በአንድ ቡድን ቁጥጥር ስር መውደቁ ታውጇል። በቪንሴንት ኮምፓኒ የሚመሩት “ባቫሪያኖቹ” የ2025/26 የውድድር ዘመን የጀርመን ቡንደስሊጋ ሻምፒዮን መሆናቸውን በይፋ አረጋግጠዋል።

​ባየር ሙኒክ ዛሬ ምሽት ስቱትጋርትን ባስተናገደበት ጨዋታ 4 ለ 2 በሆነ ውጤት ድል በመቀናጀት፣ የሊጉ የውድድር ዘመን ለማለቅ ገና 4 ጨዋታዎች እየቀሩት የዋንጫው ባለቤት መሆኑን አረጋግጧል።

ቤልጄማዊው አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ በሙኒክ ቤት የጀመረውን ጉዞ በታላቅ ድል በማጀብ የአሰልጣኝነት ጥበቡን አስመስክሯል።

​ይህ ድል ለባየር ሙኒክ በታሪኩ ለ35ኛ ጊዜ የቡንደስሊጋ ዋንጫን ወደ ካቢኔው እንዲያስገባ አስችሎታል።

​ሊጉ ሊጠናቀቅ አራት ጨዋታዎች እየቀሩ ሻምፒዮን መሆን መቻላቸው፣ ቡድኑ በዘንድሮው የውድድር ዓመት ምን ያህል ጠንካራ እና የማይበገሬ እንደነበር ማሳያ ነው።

​የሙኒክ ደጋፊዎች በአሊያንዝ አሬና እና በመላው ዓለም የድል ደስታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። የጀርመን እግር ኳስ ነገሥታት በድጋሚ በዙፋናቸው ላይ ተቀምጠዋል!

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)

#getutemesgen #getu
​#FCBayern #MiaSanMia #BundesligaChampions #VincentKompany #GermanFootball #BayernMunich #Champions2026


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: