ህወሃት ከተጠበቀው በተቃራኒ የተለሳለሰ መግለጫ አውጥቷልበምርጫ ቦርድ ህጋዊ ሰውነቱን የተነጠቀው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ…

- Advertisement -
Sidebar AD
ህወሃት ከተጠበቀው በተቃራኒ የተለሳለሰ መግለጫ አውጥቷል

በምርጫ ቦርድ ህጋዊ ሰውነቱን የተነጠቀው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሃት) ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተግባራዊነት መጓተት በትግራይ ህዝብ ላይ ከፍተኛ ስጋት እየፈጠረ መሆኑን አስታወቀ።
ኮሚቴው ከሚያዝያ 7 እስከ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ፣ በወቅታዊ ክልላዊና ብሄራዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥቷል።
📌 የፌዴራል መንግስት በስምምነቱ መሰረት የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው የመመለስና የጸጥታ ኃይሎችን የማስወጣት ግዴታውን ሙሉ በሙሉ ባለመወጣቱ፣ በትግራይ ህዝብ ላይ የሚፈጸመው ግፍና መፈናቀል መቀጠሉን ገልጿል።
📌 ድርጅቱ በውስጡ የነበሩ ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት የትግራይን ህዝብ ህልውና ለማረጋገጥና የሰላም ስምምነቱን ለማስፈጸም በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል።
📌 የፌዴራል መንግስትም ሆነ የሚመለከታቸው አካላት ስምምነቱን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲያስፈጽሙና ለትግራይ ዘላቂ ሰላም ትኩረት እንዲሰጡ ማዕከላዊ ኮሚቴው ጥሪ አቅርቧል።
​​​
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1