እኔ ስድብ አልወድም ባህላዊ ስድብ እወዳለሁ

- Advertisement -
Sidebar AD

የጨፌ ወጣቶች ሁለገብ ህብረት ስራ ማህበር ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ሰኚ ኢደሹ በአንዳፍታ ላይ ተሳዳቢ ነህ ተብሎ ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል።

ስድብ ተሳድቤ አላውቅም ያለው ሰኚ ስድቦቼ በሙሉ ዘመናዊ አይደሉም ባህላዊ ናቸው ብሏል። ሁለት አይነት ስድብ አለ ባህላዊ እና ዘመናዊ፣ በህይወቴ ተሳድቤ አላውቅም። ባህላዊ ሀገር በቀል ስድብ መሳደብ ስድብ አይደለም። “ባለጌ፣ ወርጋጥ፣ ልክስክሳም፣ ልፋጫም” ማለት ስድብ አይደለም ብሏል። በእናት፣ በብሄር፣ በኃይማኖት የምትሳደቡ ከሆነ ዘመናዊ ስድብ ነው እናንተ ተሳዳቢ ናችሁ ሲል ተናግሯል። በቲክቶክ ላይ የሚለቀቁ የኔ ቪዲዮዎች የኔ ጠንከር ያለ ምክረ ሃሳብ ነው እንጂ ስድብ አይደለም ብሏል።


Source: FastMereja

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2