በሱዳን የተማረከው የትግራይ ተወላጅ ቅጥረኛ ተዋጊ የቡርሃንን ሚስጥር አጋለጠበሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ውስጥ የተማረከው የትግራይ…

- Advertisement -
Sidebar AD
በሱዳን የተማረከው የትግራይ ተወላጅ
ቅጥረኛ ተዋጊ የቡርሃንን ሚስጥር አጋለጠ
በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ውስጥ የተማረከው የትግራይ ተወላጅ ቅጥረኛ ተዋጊ፣ የሱዳን ጦር መሪ የሆኑት አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን ጦርነቱን ለማራዘም በውጭ ሀገር ተዋጊዎች ላይ ያላቸውን ጥገኝነት የሚያጋልጥ ምስክርነት ሰጥቷል። በህወሃት እንደሰለጠነ የተነገረው ይህ ግለሰብ በሱዳን ጦር ውስጥ የታየ ብቸኛ የውጭ ተዋጊ አይደለም።
የሱዳን ጦር ጦርነቱን ለማስቀጠል የኢራን ኦፕሬቲቭንና ከሙስሊም ወንድማማቾች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ታጣቂዎች ጨምሮ የተለያዩ የውጭ ኃይላትን ይጠቀማል የሚል ክስ በተደጋጋሚ ሲቀርብበት ቆይቷል። ይህ ቅጥረኛ ተዋጊ የተማረከው በበርሊን በተካሄደው የሰላምና የሰብአዊ ድጋፍ ጉባኤ ማግስት ሲሆን፣ በጉባኤው ላይ ዓለም አቀፍ ኃይሎች ለሰብአዊ እርዳታ ድጋፍ እንደሚሰጡ ቃል በመግባት ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ ማድረጋቸው ይታወሳል።
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2