#Ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ሽሚያው እጅግ ተባብሶ በቀጠለበት በዚህ ወቅት ማንቸስተር ሲቲ ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ መሪነቱን ለያዘው አርሰናል ያለውን ቅርበት ጠብቆ መጓዝ ችሏል።
አርሰናል በ36 ጨዋታዎች 79 ነጥብ ሰብስቦ በአንደኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ማንቸስተር ሲቲ በተመሳሳይ 36 ጨዋታዎች 77 ነጥብ በመያዝ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
የሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ የጎል ልዩነትን በተመለከተ አርሰናል 42 ሲኖረው ማንቸስተር ሲቲ ደግሞ 43 አለው።
ይህ ውጤት የዘንድሮውን የፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ድል ማን ይወስደዋል የሚለውን ጥያቄ ይበልጥ አጓጊ አድርጎታል።
ዋንጫው የማነው?
#ማንቸስተርሲቲ #አርሰናል #ፕሪሚየርሊግ #እግርኳስ #ስፖርት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Source: GetuTemesgen








No comments yet.