“ ግብፅን ለማሸነፍ ብዙ ዝግጅት አድርገናል ” ዳዊት ካሳው

- Advertisement -
Sidebar AD

“ ከፈጣሪ ጋር ጨዋታውን እናሸንፋለን ” ቢኒያም አብረሀ

#Ethiopia | የኢትዮጵያ ከ 17ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን አምበል ቢኒያም አብረሀ ቡድኑ ካለፈው ውድድር በተሻለ ቁመና ላይ መሆኑን ተናግሯል።

ከሴካፋ ውድድር በኋላ ብዙ ተጨዋቾች ወደ ሊጉ ማደጋቸውን የገለፀው ቢኒያም “ ከዚህም ብዙ ተምረናል “ ብሏል።

ብሔራዊ ቡድኑ በአሁኑ ሰዓት “ በጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ጥሩ ዝግጅት አድርጓል “ ሲል ተናግሯል።

ከዚህ በፊት ኢትዮጵያ ግብፅን ማሸነፏ ተነሳሽነት ይፈጥራለቸው እንደሆነ የተጠየቀው ቢኒያም “ የእነሱን ታሪክ እንድግማለን ብለን እናስባለን “ ብሏል።

ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከጎናችን ይቁም ሲል ጥሪ ያቀረበው የቡድኑ አምበል ቢኒያም “ ፀሎት ያድርግልን ከፈጣሪ ጋር እናሸንፋለን “ብሏል።

እንደ ቲክቫህ ስፖርት ዘገባ የቡድኑ አጥቂ ዳዊት ካሳው በበኩሉ “ ዝግጅታችን ጥሩ ነው ፤ ግብፅን ለማሸነፍ ብዙ ዝግጅት አድርገናል ውጤቱን እናያለን “ ሲል ተናግሯል።

“ እንደ ሴካፋ በዚህም ውድድር የተሻለ ነገር እናደርጋለን ብዬ አስባለሁ እናልፋለን ብዬ አስባለሁ “ ዳዊት ካሳው

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1