በታገዱ ጣቢያዎች የተመዘገቡ መራጮች በልዩ ሁኔታ ድምፅ እንዲሰጡ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ወሰነ

- Advertisement -
Sidebar AD

ቀደም ሲል በተለያዩ ምክንያቶች በተዘጉ የምርጫ ጣቢያዎች ለተመዘገቡ መራጮች በምርጫው ዕለት ልዩ የምዝገባና የማረጋገጫ ሂደት ተካሂዶላቸው ድምፅ እንዲሰጡ መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

ቦርዱ ዛሬ ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ውሳኔው የዜጎችን የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብት ለማስከበርና ሂደቱን አካታች ለማድረግ ታስቦ የተወሰነ ነው ብሏል።

ቦርዱ ከዚህ ቀደም ባደረገው የክትትልና የማጣራት ሥራ የሕግ ጥሰት ተፈጽሞባቸዋል ያላቸውን 22 የምርጫ ጣቢያዎች አግዶ እንደነበር ይታወሳል።

እርምጃው የተወሰደባቸው እነዚህ ጣቢያዎች በ5 ክልሎች ማለትም፡- በኦሮሚያ 12፣ በሶማሌ 6፣ በሲዳማ 2፣ በአማራ 1፣ በሐረሪ ክልል 1 የምርጫ ጣቢያዎች ናቸው፡፡ የምርጫ ጣቢያዎቹ ሙሉ ለሙሉ ቢታገዱም፤ በእነዚህ የታገዱ ጣቢያዎች ውስጥ የተመዘገቡ ዜጎች መብታቸው ተጠብቆ በልዩ አሠራር ድምፅ የሚያስገቡበት ሁኔታ መመቻቸቱን ምርጫ ቦርድ ገልጾአል።

በፋሲል አረጋይ


Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: