ዶክተር እዮብ ተካልኝ የዓመቱ ተመራጭ የማዕከላዊ ባንክ ገዥ ሽልማት አሸናፊ ሆኑ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | የአፍሪካ ሊደርሺፕ መጽሔት የ2026 የላቀ የአፍሪካ የንግድ መሪዎች ሽልማት አሸናፊዎችን ይፋ ባደረገበት ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር እዮብ ተካልኝ የዓመቱ ምርጥ የማዕከላዊ ባንክ ገዥ በመሆን ተመርጠዋል።

ዶክተር እዮብ ተካልኝ ይህንን ታላቅ የዘርፉን የቀዳሚነት ክብር ከታንዛኒያው አማኑኤል ቱቱባ ጋር በጋራ የተጋሩት ሲሆን በዚሁ መርሃግብር የኢትዮጵያ አየር መንገድ የዓመቱ ምርጥ የአፍሪካ ብራንድ ተብሎ በመመረጥ ሌላ ታሪካዊ ስኬት አስመዝግቧል።

በሕዝብ አስተያየትና በተቋማዊ ግምገማ አሸናፊ መሆን የቻሉት እነዚህ የኢትዮጵያ ተቋማትና መሪዎች እንደ ዳንጎቴ ግሩፕ እና ማስተርካርድ ካሉ የአህጉሪቱ ታዋቂ ተቋማት ጋር በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን ሽልማታቸውን በቀጣዩ ሐምሌ ወር በለንደን በሚካሄድ ደማቅ ሥነ ሥርዓት ላይ እንደሚረከቡ ታውቋል።

#Ethiopia #AfricanLeadership #BusinessLeaders2026 #EthiopianAirlines #EconomicExcellence #AfricaProud #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa



Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: