#Ethiopia | ዛሬ በሚካሄደው ከፍተኛ ግምት የተሰጠው የስፖርት ውድድር ምክንያት የቡዳፔስት ፖሊስ መምሪያ የከተማዋን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ በርካታ የፖሊስ አባላትን በተጠንቀቅ ማሰማራቱን አስታወቀ።
የፖሊስ መምሪያው ባወጣው መግለጫ፣ ጨዋታው በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅና ሊፈጠሩ የሚችሉ ማናቸውንም ግርግሮች ለመከላከል የጸጥታ ኃይሉ በከፍተኛ ዝግጁነት ላይ እንደሚገኝ አሳስቧል።
በስታዲየሙ ዙሪያ፣ በሕዝብ ማጓጓዣ ጣቢያዎች እና ደጋፊዎች በብዛት በሚሰበሰቡባቸው የአደባባይ ቦታዎች ላይ ቁጥራቸው የበዛ የፖሊስ አባላት ተሰማርተዋል።
በጨዋታው ወቅትና ከጨዋታው በኋላ በስታዲየሙ አቅራቢያ ባሉ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የትራፊክ ፍሰት ለጊዜው ሊገደብ ወይም አቅጣጫ ሊቀየር እንደሚችል ተገልጿል።
በደጋፊዎች መካከል ሊነሳ የሚስልን ግጭት ለማስቀረት የሁለቱም ወገን ደጋፊዎች ወደ ስታዲየም የሚገቡባቸውና የሚወጡባቸው መንገዶች ተለይተው ጥብቅ ቁጥጥር ይደረግባቸዋል።
“የከተማዋ ነዋሪዎችና ለጨዋታው የሚመጡ ደጋፊዎች ከጸጥታ አካላት ጋር ሙሉ ትብብር እንዲያደርጉ፣ እንዲሁም አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ በአስቸኳይ ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጡ እናሳስባለን።”
የዛሬው ጨዋታ በደማቅ ስፖርታዊ ጨዋነት እንዲጠናቀቅና በከተማዋ የእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ መስተጓጎል እንዳይፈጠር ፖሊስ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ጥብቅ ክትትሉን እንደሚቀጥል አስታውቋል።
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Source: GetuTemesgen









No comments yet.