ወደ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ሊገባ የነበረ ሞባይል ስልክ በፍተሻ ተያዘገሊላ | ግንቦት 22/2018 ዓ/ም(ኣሪ ማህበረሰብ ሬዲዮ)፦…

- Advertisement -
Sidebar AD
ወደ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ሊገባ የነበረ ሞባይል ስልክ በፍተሻ ተያዘ
ገሊላ | ግንቦት 22/2018 ዓ/ም(ኣሪ ማህበረሰብ ሬዲዮ)፦  በዲላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ለታራሚ ሊገባ የነበረ ሞባይል ስልክ በተደረገ ጥብቅ ፍተሻ መያዙን ተቋሙ አስታውቋል።
ወ/ሪት ንግስት ይጨነቁ የተባለች የህግ ታራሚ ዘመድ ጠያቂ በመምሰል ወደ ተቋም እንዳይገባ የተከለከለ ሞባይል ስልክ በእግሯ ላይ በማሰር ለማስገባት ስትሞክር በዕለቱ ተረኛ ሴት ፈታሽ ፖሊስ በተደረገ ጥብቅ ፍተሻ ተይዛለች።
የተቋሙ አዛዥ ኢንስፔክተር ትዕግስት ሮቤ እንደገለፁት የህግ ታራሚ ዘመድ ጠያቂዎች ለማረም ማነጽ ስራ አጋዥ መሆን ስገባ ይህን ያህል አስነዋሪ ተግባር መፈጸም ተገቢ አለመሆኑን አሳስበው ወ/ሪት ንግስት ይጨነቁ በዲላ ከተማ ፖሊስ ምርመራ እንዲጣራ መላኳን አስታውቀዋል።
በስተመጨረሻ የተከበረው የዲላ ከተማና አከባቢዋ ነዋሪዎች የማረም ማነጽ ተግባር የሁሉ ዜጋ ኃላፊነት መሆኑን በመገንዘብ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
Via South Police
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: