‹‹ብልጽግና እና ሕውሓት ኤርትራን በጋራ ለማጥቃት ተነጋግረው ነበር›› ሻብያየኤርትራ መንግስት አዲስ እና ያልተሰማ ትርክት ይዞ…

- Advertisement -
Sidebar AD
‹‹ብልጽግና እና ሕውሓት ኤርትራን በጋራ ለማጥቃት ተነጋግረው ነበር›› ሻብያ
የኤርትራ መንግስት አዲስ እና ያልተሰማ ትርክት ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ እና አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከሰሞኑ አልጀዚራ ላይ ያጋሩትን ጽሁፍ ተከትሎ ከአስመራ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ የአገሪቱ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል፣ በጽሁፉ ላይ የቀረቡትን ሁሉንም ክሶች አጣጥለዋል፡፡
የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ምላሽ የባለሥልጣናትን ንግግር “በሐሰት፣ በማታለልና በተሳሳተ መረጃ የተሞላ” ሲሉ አጣጥለውታል። አቶ የማነ ምላሻቸው በመቀጠል ይልቁንም ዛሬ ክስ እያቀረቡብን ያሉት አካላት “የፕሪቶሪያው ስምምነት ከመፈረሙ ከጥቂት ወራት በፊት በጅቡቲ እና ሲሸልስ በሚስጥር ተገናኝተው በኤርትራ ላይ የጋራ ወረራ ለመፈጸም ሲዶልቱ ነበር” በማለት ከዚህ በፊት ያልተሰማ ሌላ አዲስ ትርክት ይዘው መጥተዋል።
አንዳፍታ
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: