”ወላጅ እናቱ በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ታዳጊ በቁጥጥር ስር ዋለ” ደብረብርሃን ፖሊስ መምሪያ
በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር፣ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ፣ አየር ጤና ቀበሌ ውስጥ ወላጅ እናቱን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የተጠረጠረው ወጣት ዮሴፍ ከበደ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ።
የክፍለ ከተማው ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ሟች ወ/ሮ ፍሬህይወት ገብረሚካኤል ተከራይታ ትኖርበት የነበረውን የተቆለፈ ቤት በር ሰብሮ በመግባት ባደረገው ፍተሻ፤ ሟች አንገቷ በቢላ ተቆርጦና ለብቻው በማዳበሪያ ተቋጥሮ መገኘቱን አስታውቋል።
በፖሊስ የመጀመሪያ ደረጃ ማጣራት ግድያው የተፈፀመው ሰኔ 08 ቀን 2018 ዓ.ም አካባቢ ሲሆን፣ የቤቱ የውጭ በርም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ተቆልፎ ሰንብቷል።
ፖሊስ አስከሬኑን ካነሳ በኋላ ባደረገው ፈጣን ክትትል፣ ወንጀሉን ፈፅሞ ወደ አዲስ አበባ የሸሸውና የ”666″ አባል እንደሆነ የተነገረለት የሟች ልጅ ዮሴፍ ከበደ፤ ተመልሶ አክስቱ ቤት ተደብቆ ሳለ ወንጀሉን ከፈፀመበት ቢላ ጋር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል።
የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን እየተመኘ ይህ አሰቃቂ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ሌት ተቀን በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጧል።
Via:- ደብረብርሃን ፖሊስ መምሪያ
@Seledadotio
@Seledadotio
በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር፣ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ፣ አየር ጤና ቀበሌ ውስጥ ወላጅ እናቱን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የተጠረጠረው ወጣት ዮሴፍ ከበደ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ።
የክፍለ ከተማው ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ሟች ወ/ሮ ፍሬህይወት ገብረሚካኤል ተከራይታ ትኖርበት የነበረውን የተቆለፈ ቤት በር ሰብሮ በመግባት ባደረገው ፍተሻ፤ ሟች አንገቷ በቢላ ተቆርጦና ለብቻው በማዳበሪያ ተቋጥሮ መገኘቱን አስታውቋል።
በፖሊስ የመጀመሪያ ደረጃ ማጣራት ግድያው የተፈፀመው ሰኔ 08 ቀን 2018 ዓ.ም አካባቢ ሲሆን፣ የቤቱ የውጭ በርም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ተቆልፎ ሰንብቷል።
ፖሊስ አስከሬኑን ካነሳ በኋላ ባደረገው ፈጣን ክትትል፣ ወንጀሉን ፈፅሞ ወደ አዲስ አበባ የሸሸውና የ”666″ አባል እንደሆነ የተነገረለት የሟች ልጅ ዮሴፍ ከበደ፤ ተመልሶ አክስቱ ቤት ተደብቆ ሳለ ወንጀሉን ከፈፀመበት ቢላ ጋር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል።
የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን እየተመኘ ይህ አሰቃቂ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ሌት ተቀን በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጧል።
Via:- ደብረብርሃን ፖሊስ መምሪያ
@Seledadotio
@Seledadotio









No comments yet.