አሜሪካ እና ኢራን የተኩስ አቁምን በመጣስ አንዳቸው ሌላቸውን እየከሰሱ ነው

- Advertisement -
Sidebar AD

አሜሪካ እና ኢራን ተኩስ መለዋወጣቸውን ተከትሎ የተኩስ አቁምን በመጣስ አንዳቸው ሌላቸውን እየከሰሱ ነው።
በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል እያለፈ የነበረ በፓናማ የተመዘገበ መርከብ ትናንት ቅዳሜ ጥቃት ከደረሰበት በኋላ አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት ፈጽማለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ በንግድ መርከቦች ላይ “ትንኮሳ ስለቀጠለ” በኢራን በርካታ ዒላማዎችን መምታቱን አስታውቋል።

የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በአጸፋ ምላሽ በኩዌት እና ባሕሬን በሚገኙ የአሜሪካ መሠረተ ልማቶች ላይ የድሮን እና ሚሳዔል ጥቃቶች ማድረሱን ገልጿል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ባወጣው መግለጫ “ኢራን የተኩስ አቁሙን እንድታከብር ዕድል ተሰጥቷት ነበር። ጦሯ የድሮን ጥቃት በማድረስ ስምምነቱን መጣስን መርጧል” ብሏል።
የአሜሪካ ተዋጊ ጄቶች በ10 የኢራን ወታደራዊ ዒላማዎች ላይ ድብደባ ማድረሳቸውን አስታውቋል። በሆርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ የተፈጸሙት ጥቃቶች የመገናኛ ሥርዓቶች፣ የአየር መከላከያዎች እና የድሮን ማከማቻ ላይ ያነጣጠሩ ናቸው ተብሏል።

የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ባወጣው መግለጫ፤ አሜሪካ በአምስት የባሕር ዳርቻ ይዞታዎች ላይ ጥቃድ ማድረሷን ገልጿል።
“በኩዌት አሊ አል-ሳሊም ወታደራዊ መቀመጫ እና በባሕሬን ፊፍዝ ናቫል ፍሊት የሚገኙ ስምንት ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የአጸፋ እርምጃ ተወስዷል” ሲልም አክሏል።

BBC



Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: