የአቶ ሀይሉ ሀብተሚካኤል አጭር የሕይወት ታሪክ
#Ethiopia | አቶ ሀይሉ ሀብተሚካኤል ከአባታቸው ከአቶ ሀብተሚካኤል አስናቀ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አበበች ገ/ጻዲቅ በሰሜን ሸዋ፣ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ፣ ልዩ ስሙ ደግማት በተባለ ሥፍራ መስከረም 19 ቀን 1940 ዓ.ም ተወለዱ።
ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።
ወደ ሥራ ዓለም በመግባትም በ1964 ዓ.ም በኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ፋብሪካ (ፔፕሲ ) ተቀጥረው፣ በታማኝነትና በትጋት እስከ ጡረታ ዘመናቸው ድረስ አገልግለዋል።
በትዳር ሕይወታቸው ከወ/ሮ አመለወርቅ ተክሉ ጋር ትዳር መስርተው 5 ወንድና 2 ሴት (በአጠቃላይ 7) ልጆችን አፍርተዋል፤ እንዲሁም 13 የልጅ ልጆችን ለማየት በቅተዋል።
አቶ ሀይሉ በእርጅናና በሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው፣ በተወለዱ በ78 ዓመታቸው ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የክቡር አባታችን የ ሥነ ሥርዓት ነገ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ላይ በቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ይፈጸማል።


Source: GetuTemesgen









No comments yet.