#FastMereja I ከኛንጋቶም ወረዳ የመጡት ዶክተር ሶያ ኩሩፓ፣ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ በህክምና ሙያ በመመረቅ የህዝባቸው የመጀመሪያው የህክምና ዶክተር በመሆን ታሪክ ሰርተዋል። ዶክተር ሶያ፣ ለሰባት ዓመታት የዘለቀው አስቸጋሪ የትምህርት ጉዞ፣ ለወደፊት ለሚመጡት የገጠር ወጣቶች ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል።
ዶክተር ሶያ ኩሩፓ፣ የተወለዱትና ያደጉት በኛንጋቶም ወረዳ በሚገኝ ራቅ ያለ አርብቶ አደር ማህበረሰብ ውስጥ ነው። በዚያ አካባቢ የትምህርትና የጤና አገልግሎት አቅርቦት እጅግ ውስን በሆነበት ሁኔታ ውስጥ ማደግ፣ የህክምና ዶክተር የመሆንን ህልም የሩቅ ተስፋ አድርጎት እንደነበር ያስታውሳሉ።
ይሁን እንጂ በቤተሰብ፣ በማህበረሰብ እና በአማካሪዎች ድጋፍ፣ እንዲሁም በራሳቸው የጽናት ብርታት ሰባት ዓመታትን በጅማ ዩኒቨርሲቲ በማሳለፍ የህክምና ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። ይህ ስኬት የግል ድል ብቻ ሳይሆን፣ የቤተሰባቸው፣ የኛንጋቶም ህዝብ እና ለመላው የገጠር ማህበረሰብ የሚተርፍ የትምህርት ተምሳሌት መሆኑን ተናግረዋል።
ዶክተሩ አክለውም፣ ይህ ስኬት ሌሎች ወጣቶች ከኋላ የመጡበት ሁኔታ የአቅማቸውን ጣሪያ መወሰን እንደሌለበት ማሳያ ነው ብለዋል። በሙያ ዘመናቸውም በተለይ ለጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለሚቸገሩ አካባቢዎች ቅድሚያ በመስጠት እንደሚያገለግሉ ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
Source: FastMereja









No comments yet.