ፖሊስ መስላ በፊቼ ከተማ ስትዘርፍ የነበረችው ሴት በቁጥጥር ስር ዋለች

- Advertisement -
Sidebar AD

​#FastMereja I ​በሰሜን ሸዋ ዞን የፊቼ ከተማ አስተዳደር፣ የፖሊስ የደንብ ልብስ በመልበስ እና የጦር መሳሪያ በመያዝ የዘረፋ ወንጀል ስትፈጽም የነበረች ሴት በቁጥጥር ስር ዋለች።

ተጠርጣሪዋ አበባ ቁንቢ ትባላለች። ​የፊቼ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ምክትል ኢንስፔክተር ቶልቻ ኃይሉ ለቢቢሲ እንደገለጹት፣ ተጠርጣሪዋ የፖሊስ የደንብ ልብስ በመልበስ እና ሽጉጥ በመታጠቅ የተለያዩ የዘረፋ ወንጀሎችን ስትፈጽም ቆይታለች።

​በተለያዩ የንግድ ተቋማት በመሄድ የዞን ፖሊስ መምሪያ አባል ነኝ ገንዘብ ረስቼ ወጥቼ ነው በማለት የምትፈልገውን ከሱቅ ትወስዳለች።

​እምነት ለማትረፍ ስትል የራሷን ፎቶ እና ሽጉጥ ታጥቃ የተነሳችውን ምስል በማሳየት እቃዎችንና አልባሳትን በግድ ትወስድ እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል።

​በሌላ በኩል፣ ሌሊትን በመጠቀም ከሌሎች ተባባሪዎቿ ጋር በመሆን ሰዎችን በጦር መሳሪያ በማስፈራራት ስትዘርፍ እንደነበር ምርመራው አረጋግጧል።

​ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት ፖሊስ ክትትል በማድረግ ተጠርጣሪዋን ተከራይታ በምትኖርበት ቤት ውስጥ ከ​አንድ የቱርክ ሽጉጥ፣ ​አንድ የወገብ ካርታ፣​ሁለት የክላሽንኮቭ ጥይት ካርታ፣ ​አንድ ጎራዴ፣ ​ከተለያዩ የፖሊስ የደንብ ልብሶች እና ሶስት የፖሊስ ዱላዎች ጋር በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተጣራባት እንደሚገኝና ለህግ እንደምትቀርብ የፊቼ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል።

#ችሎት


Source: FastMereja

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: