ኢትዮጵያ በጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ እና ኢንዶኔዥያ አዳዲስ የባህር ትራንስፖርት መስመሮች ጀመረችየኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎ…

- Advertisement -
Sidebar AD
ኢትዮጵያ በጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ እና ኢንዶኔዥያ አዳዲስ የባህር ትራንስፖርት መስመሮች ጀመረች
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በበጀት ዓመቱ ወደ ጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ እና ኢንዶኔዥያ አዳዲስ የጉዞ መስመሮችን በመክፈት የንግድ ትስስሩን እያጠናከረ እንደሚገኝ አስታውቋል።
የተቋሙ የኮርፖሬት ማርኬቲንግ መምሪያ ኃላፊና የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ተወካይ አቶ ደምሰው በንቲ፣ በኢንዶኔዥያና በጃፓን መስመሮች ላይ ከባድ ማሽነሪዎችን፣ ተሽከርካሪዎችንና የኮንስትራክሽን መሣሪያዎችን የማጓጓዝ ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ለጋዜጣ ፕላስ ገልጸዋል።
ኃላፊው አክለውም፣ ወደፊትም የደንበኞችንና የሀገሪቱን ጥቅም ማዕከል ያደረጉ አዳዲስ መዳረሻዎችን የማስፋፋት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
እነዚህ አዳዲስ የባህር መስመር ጉዞዎች መጀመራቸው የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ ያሻሽላል ያሉት አቶ ደምሰው፣ የወደብ ጭነቶች በአጭር ጊዜ ወደተፈለገው ቦታ እንዲደርሱ በማስቻል ጊዜንና ወጪን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቆጥብ አስገንዝበዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: