#Ethiopia | የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር አስናቀ አበበ እንደሚያስረዱት፤ ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ በግብረ-ስጋ ግንኙነትና ወቅት የመተላለፍ እድሉ ከኤች.አይ.ቪ (HIV) ጋር ሲነጻጸር እስከ 30 እጥፍ ይበልጣል።
በሀገራችን ከ9 እስከ 10 በመቶ የሚሆነው ህዝብ በዚህ ቫይረስ እንደሚያጠቃ መረጃዎች ያሳያሉ።
ስለሆነም ራሳችንንና ወዳጆቻችንን ከዚህ በሽታ ለመጠበቅ እንዲሁም በበሽታው የተያዙ ሰዎች ማድረግ የሚገባቸው ዋና ዋና የምክር ነጥቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡
1. ቅድመ-ጥንቃቄና መከላከያ መንገዶች
የጥንቃቄ አሰራርን መከተል፦
ሄፓታይተስ ቢ እና ሲ በግብረ ስጋ ግንኙነት የሚተላለፍ እንደመሆኑ ልክ ለኤች.አይ.ቪ እንደሚደረገው ሁሉ በግብረ-ስጋ ግንኙነት ወቅት ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እና በደም የተበከሉ ስለታም ቁሳቁሶችን ከሌሎች ጋር አለመጋራት ያስፈልጋል።
ሄፓታይተስ ቢ ክትባት መከተብ፦ በደማቸው ውስጥ ቫይረሱ የሌለባቸው ሰዎች ቀድመው የሄፐታይቲስ ቢ ክትባትን በመውሰድ ሙሉ በሙሉ መከላከል ይችላሉ።
2. የበሽታውን ምልክቶች በጥንቃቄ መከታተል
የበሽታው ምልክቶች በሁለት ተከፍለው ይታያሉ፡
*በአጭር ጊዜ የሚታዩ ምልክቶች፦
የሰውነት ትኩሳት፣ ማቅለሽለሽ፣ የቆዳና የዓይን ቢጫ መሆን።
*በረጅም ጊዜ (Chronic – ከ6 ወር በላይ) የሚታዩ ምልክቶች፦
የሰውነት ድካምና ማበጥ፣ ደም ማስታወክ፣ የመንገዳገድ ስሜት እና የሰገራ መጥቁር።
3. ለተያዙ ሰዎች የሚሰጥ የህክምና ምክር
ቋሚ የህክምና ክትትል፦
ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ለረጅም ጊዜ (ከስድስት ወር በላይ) የሚገኝባቸው ሰዎች (Chronic Hepatitis) ቫይረሱ ጉበት ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ቋሚ የህክምና ክትትል ማድረግ ይኖርባቸዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Source: GetuTemesgen









No comments yet.