የደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ታሪካዊ ቴአትር በትውልድ ስፍራቸው ወሊሶ ሊቀርብ ነው

- Advertisement -
Sidebar AD


‎#Ethiopia | ​የዓድዋውን ጀግና የደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶን አኩሪ ታሪክ እና ገድል የሚያወሳው ታዋቂው ቴአትር በጀግናው ትውልድ ስፍራ በወሊሶ ከተማ ለህዝብ ለእይታ ሊቀርብ ተጠናቀቀ።

ይህ ታላቅ የኪነ-ጥበብ ኩነት እውን ሊሆን የቻለው የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ከወሊሶ ከተማ አስተዳደር እና ከጀግናው ቤተሰቦች ጋር ባደረጉት ትብብር ሲሆን፣ ሁለቱ አካላት ስራውን በጋራ ለማቅረብ የሚያስችላቸውን ታሪካዊ የስራ ስምምነት ተፈራርመዋል።

‎​ስምምነቱ የጀግናውን ታሪክ በትውልድ ስፍራው ከመዘከር ባሻገር በወሊሶ ከተማ የኪነ-ጥበብ ስራዎችን በስፋት ለማስተዋወቅ እና ለማሳደግ ትልቅ መንገድ የሚከፍት ነው።

‎በብዙዎች በጉጉት የሚጠበቀው ይህ “ባልቻ አባ ነፍሶ” ቴአትር በቅርቡ ለወሊሶ እና ለአካባቢው ነዋሪዎች በመድረክ የሚቀርብ ሲሆን፣ የጀግኖቻችንን ታሪክ በኪነ-ጥበብ ህያው በማድረግ ለተከታታዩ ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስችል ይታመናል።

‎#BalchaAbaNafso ​#EthiopianHistory ​#AdwaHero ​#Woliso ​#EthiopianTheatre
​#EthiopianArts ​#AddisAbabaTheatre






Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2