የነገሌ አርሲ የፖሊስ አባል በፈራረሠ ቤት ተጥሎ በረሃብ ተዳክሞ የተገኘ ሕፃን አንስታ ጡታን በማጥባት ከሞት ታደገችውበምዕራብ …

- Advertisement -
Sidebar AD
የነገሌ አርሲ የፖሊስ አባል በፈራረሠ ቤት ተጥሎ በረሃብ ተዳክሞ የተገኘ ሕፃን አንስታ ጡታን በማጥባት ከሞት ታደገችው
በምዕራብ አርሲ ዞን ነገሌ አርሲ ወረዳ ቱሉ ቀበሌ በፈራረሠ ቤት ተጥሎና በረሐብ ምክንያት ተዳክሞ የተገኘን ሕፃን የተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ ጥቆማ ያደርጋሉ።
ጥቆማ ከደረሣቸው የነገሌ አርሲ ወረዳ ፖሊሶች መካከል ኢንስፔክተር ጉደቱ ኡሊ የተባለችው ገና ሕፃኑን ስታይ በረሐብ የተዳከመ መሆኑን አይታ ቶሎ ከመሬት አንስታ ጡታን በማጥባት ከሞት የታደገች መሆኑን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ማንነቷ ለጊዜው ባልታወቀች እናት የተጣለው የሑለት ወር ሕፃን በባዶና በፈራረሰ ቤት ሲያለቅስ የሠሙ ሠዎች ለፖሊስ በሠጡት ጥቆማ ሕፃኑ በረሐብ የተዳከመ የነበረ ሲሆን በኢንስፔክተር ጉደቱ ኡሊ መልካም ተግባር ጡቷን በመጥባት ሊያገግም ችሏል።
 
የፖሊስ መኮንኗ በፈፀመችው መልካም የእናትነት ተግባር ያገገመው የሑለት ወር ሕፃን  በጤና ተቋም የተመጣጠነ ምግብ አግኝቶ በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2