በታላቋ ገዳም በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ድንገት በተከሰተ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰው ሕይወት አለፈ።
በመሬት መንሸራተቱ የ14 ምዕመናን ሂወት ሲያልፍ በ5 ሰው ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በ2 ሰዎች ላይ መለስተኛ ጉዳት በመድረሱ የወረዳዉ አስተዳደር ምክርቤት መሪር ኀዘኑን ገልፆል ።
የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ የማነብርሀን ተስፈ ጨምሮ የወረዳ አስተባባሪ አመራርና የፀጥታ አመራሩ እቦታዉ ላይ በመገኘት ነፍስ በማዳን እርብርቡ ላይ ሁለተናዊ ድጋፍ አድርገዋል።
የህክምና ባለሙያዎች የአካባቢዉ ማህበረሰብ በቦታዉ ላይ በመገኘት የተጎዱ ወገኖችን የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ብርቱ ትግል አድርገዋል።
ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ በስፍራው የተገኙ ሲሆን ለሞቱ ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት ለተጎዱት ጸሎት ላዘኑ ወገኖቻችን የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ።
Source: FastMereja









No comments yet.