የአነስተኛ ገንዘብ ኖቶች እጥረት‼️
የአነስተኛ የገንዘብ ኖቶች እጥረት የችርቻሮ ነጋዴዎችን እና ደንበኞችን እየፈተነ ይገኛል።
በኢትዮጵያ የችርቻሮ ንግድ ዘርፍ አነስተኛ የገንዘብ ኖቶች በተለይም የ 10 ብር ኖት እጥረት በዕለታዊ የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ነው። በርካታ የሱቅ ባለቤቶች መልስ በማጣታቸው ምክንያት ደንበኞችን ለመመለስ ወይም እቃዎችን በዕዳ ለመስጠት ተገደዋል።
የአገሪቱ አጠቃላይ የዋጋ ንረት 13.9% እንዲሁም የምግብ ዋጋ ንረት 15.1% በመድረሱ፣ አነስተኛ ኖቶች በእጅ የመዘዋወር ፍጥነታቸው ጨምሮ በፍጥነት እንዲያልቁና እንዲቀደዱ አድርጓል። እ.ኤ.አ በ 2020 ከተደረገው የብር ቅያሬ ወዲህ አዲስ የ 10 ብር ኖት ያልታተመ በመሆኑም በገበያው ላይ ያለው መጠን በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መጥቷል።
በተጨማሪም ከ 350 ቢሊዮን ብር በላይ ከባንክ ሥርዓት ውጭ በህዝብ እጅ ስለሚገኝ፣ ብሔራዊ ባንክ ያረጁ ኖቶችን ሰብስቦ ለመተካትና ለማስወገድ ተቸግሯል። እስከ እ.ኤ.አ 2030 ሙሉ በሙሉ ከጥሬ ገንዘብ ነፃ የመሆን ግብ ቢኖርም፣ የኤሌክትሪክ እና የቴሌኮም መቆራረጥ እንዲሁም የዲጂታል መሣሪያዎች ውድነት ሽግግሩን እያዘገየው ይገኛል።
”የአነስተኛ ኖቶች እጥረት የዘወትር ራስ ምታት ሆኖብናል። አንዳንድ ጊዜ ደንበኞችን መልሰን እንልካለን፤ ወይም ዕቃዎችን በብድር ለመስጠት እንገደዳለን።” ሲሉ ተደምጠዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio
የአነስተኛ የገንዘብ ኖቶች እጥረት የችርቻሮ ነጋዴዎችን እና ደንበኞችን እየፈተነ ይገኛል።
በኢትዮጵያ የችርቻሮ ንግድ ዘርፍ አነስተኛ የገንዘብ ኖቶች በተለይም የ 10 ብር ኖት እጥረት በዕለታዊ የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ነው። በርካታ የሱቅ ባለቤቶች መልስ በማጣታቸው ምክንያት ደንበኞችን ለመመለስ ወይም እቃዎችን በዕዳ ለመስጠት ተገደዋል።
የአገሪቱ አጠቃላይ የዋጋ ንረት 13.9% እንዲሁም የምግብ ዋጋ ንረት 15.1% በመድረሱ፣ አነስተኛ ኖቶች በእጅ የመዘዋወር ፍጥነታቸው ጨምሮ በፍጥነት እንዲያልቁና እንዲቀደዱ አድርጓል። እ.ኤ.አ በ 2020 ከተደረገው የብር ቅያሬ ወዲህ አዲስ የ 10 ብር ኖት ያልታተመ በመሆኑም በገበያው ላይ ያለው መጠን በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መጥቷል።
በተጨማሪም ከ 350 ቢሊዮን ብር በላይ ከባንክ ሥርዓት ውጭ በህዝብ እጅ ስለሚገኝ፣ ብሔራዊ ባንክ ያረጁ ኖቶችን ሰብስቦ ለመተካትና ለማስወገድ ተቸግሯል። እስከ እ.ኤ.አ 2030 ሙሉ በሙሉ ከጥሬ ገንዘብ ነፃ የመሆን ግብ ቢኖርም፣ የኤሌክትሪክ እና የቴሌኮም መቆራረጥ እንዲሁም የዲጂታል መሣሪያዎች ውድነት ሽግግሩን እያዘገየው ይገኛል።
”የአነስተኛ ኖቶች እጥረት የዘወትር ራስ ምታት ሆኖብናል። አንዳንድ ጊዜ ደንበኞችን መልሰን እንልካለን፤ ወይም ዕቃዎችን በብድር ለመስጠት እንገደዳለን።” ሲሉ ተደምጠዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio
Related Posts
- Advertisement -









No comments yet.