ኦሪገን 2026፦ ኢትዮጵያ በወንዶች 5,000 ሜትር የነሐስ ሜዳሊያ አሸነፈች

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | በኦሪገን፣ አሜሪካ እየተካሄደ ባለው የ2026 የዓለም ከ20 ዓመት በታች (World U20) ሻምፒዮና የመጀመሪያ ቀን ውድድር፣ በወንዶች 5,000 ሜትር ፍፃሜ ኬንያ የወርቅና የብር ሜዳሊያዎችን ስታሸንፍ፣ ኢትዮጵያ በነሐስ ሜዳሊያ ተወስናለች።

ኬንያዊው ፍራንክላይን ኪቤት 13:28.27 በሆነ ሰዓት ውድድሩን በማሸነፍ የዓለም ከ20 ዓመት በታች የ5,000 ሜትር ሻምፒዮን ሆኗል። ይህም ባለፈው ጥር ወር ያሸነፈውን የዓለም የአገር አቋራጭ (Cross Country) የU20 ዋንጫ ተከትሎ ያስመዘገበው ሌላ ትልቅ ስኬት ነው።

ኔሄሚያ ኪፕንጌኖ 13:30.09 በመሮጥ ለኬንያ የብር ሜዳሊያን ሲያስገኝ፣ ኢትዮጵያዊው ዳምጠው ከበደ 13:35.38 በሆነ ሰዓት የነሐስ ሜዳሊያን አሸንፏል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ማማሩ ጎአዲ 13:44.41 በሆነ ሰዓት አምስተኛ ደረጃን ይዟል።

በዚህ ውጤት ኬንያ በዓለም የU20 ሻምፒዮና የ5,000 ሜትር ታሪካዊ የወርቅ ሜዳሊያ ብዛት 11 በማድረስ ኢትዮጵያን 10 ሻምፒዮንነቶች በመብለጥ ቀዳሚነቷን አጠናክራለች።

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)




Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2