“ያለ አምላክ እምነት የሰው ልጅ ምሉዕ ሊሆን አይችልም” — ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | ​የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ሃይማኖት በማህበረሰብ ህይወት ውስጥ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው ክርስቲያኖችም ሆኑ ሙስሊሞች በአንድ አምላክ የሚያምኑ በመሆናቸው የቤተክርስቲያናት እና የመስጊዶችን ግንባታ ሲደግፉ መቆየታቸውን አስታወቁ።

​ፕሬዚዳንቱ አክለውም ሃይማኖት ለሰዎች በጎ እሴቶችን፣ መሪ መመሪያን እና ግልጽ የህይወት አቅጣጫን እንደሚሰጥ በመጠቆም መንፈሳዊ እምነት ከሰው ልጅ ህይወት ጋር የማይነጠል አካል መሆኑን አብራርተዋል።

አምላክን ማመን የሰው ልጅነት መሠረት መሆኑን ያሰመሩበት ሩቶ “ሰው ያለ አምላክ እምነት ሙሉ ሊሆን አይችልም” ሲሉ የማህበረሰቡን መንፈሳዊ ጥንካሬ እና የእምነት ተቋማትን አስፈላጊነት አጉልተው አሳይተዋል።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)

#getutemesgen #getu


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2