#Ethiopia | የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ሃይማኖት በማህበረሰብ ህይወት ውስጥ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው ክርስቲያኖችም ሆኑ ሙስሊሞች በአንድ አምላክ የሚያምኑ በመሆናቸው የቤተክርስቲያናት እና የመስጊዶችን ግንባታ ሲደግፉ መቆየታቸውን አስታወቁ።
ፕሬዚዳንቱ አክለውም ሃይማኖት ለሰዎች በጎ እሴቶችን፣ መሪ መመሪያን እና ግልጽ የህይወት አቅጣጫን እንደሚሰጥ በመጠቆም መንፈሳዊ እምነት ከሰው ልጅ ህይወት ጋር የማይነጠል አካል መሆኑን አብራርተዋል።
አምላክን ማመን የሰው ልጅነት መሠረት መሆኑን ያሰመሩበት ሩቶ “ሰው ያለ አምላክ እምነት ሙሉ ሊሆን አይችልም” ሲሉ የማህበረሰቡን መንፈሳዊ ጥንካሬ እና የእምነት ተቋማትን አስፈላጊነት አጉልተው አሳይተዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Source: GetuTemesgen









No comments yet.