በጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል የ26 ዓመቷ እናት አራት ሕፃናትን በሰላም ተገላገለች

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | ​በአዲስ አበባ በሚገኘው ጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል የ26 ዓመት ወጣት እናት በአንድ ጊዜ አራት ሕፃናትን በሰላም ማገላገሉን የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

በአሁኑ ወቅት እናትየዋና አራቱም ጨቅላ ሕፃናት በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።

​የሕክምና ሂደቱን በበላይነት የመሩት የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅና የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር እሸቱ ታደለ እንደገለጹት፣ የእርግዝናው ሁኔታ አስቀድሞ በክትትል በመታወቁ እናቲቱ ከወሊድ ቀኗ አንድ ወር በፊት በሆስፒታሉ ተኝታ ሌት ተቀን ጥብቅ ክትትል ሲደረግላት ቆይታለች።

የሆስፒታሉ የሕክምና ቡድን በከፍተኛ የሕክምና ቴክኖሎጂና አጋዥ መሳሪያዎች የታገዘ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ቀዶ ሕክምናውን በስኬት ማጠናቀቅ ችሏል።

ዶክተር እሸቱ አክለውም ይህ አጋጣሚ “እናት ጤና፤ ልጅም ደህና” የሚለውን ሀገራዊ የጤና መርሕ በተግባር ለማዋል የተከናወነና ለእናቶችና ሕፃናት ጤና የተሰጠውን ትልቅ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)

#getutemesgen #getu


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: