ኮሜዲያን ያሲኖ የ”ቤተሰብ ጨዋታ” አቅራቢ ሆኖ ተመረጠ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | ​የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ለረጅም ጊዜ በስክሪን ላይ የቆየውንና በብዙዎች ዘንድ የሚወደደውን “ቤተሰብ ጨዋታ” ዝግጅት በዋና አቅራቢነት እንዲመራ ኮሜዲያን ያሲኖን በተመልካቾች መረጠ።

የዝግጅቱ የረጅም ጊዜ አቅራቢ የነበረው አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ተከትሎ ኢቢኤስ አዲስ አቅራቢ ለመተካት በተለያዩ አርቲስቶች እና ኮሜዲያኖች መካከል አቅም የመለካት ውድድር ሲያካሂድ ቆይቷል።

ተወዳዳሪዎቹ በስቱዲዮ ውስጥ ባሳዩት የዝግጅት አቀራረብ ብቃት እና ከተመልካች በተሰበሰበ የኤስኤምኤስ (SMS) ድምጽ መሰረት ኮሜዲያን ያሲኖ ከመጨረሻዎቹ አራት እጩዎች መካከል በከፍተኛ የድምጽ ልዩነት ማሸነፉ ተረጋግጧል።

አሸናፊነቱን ተከትሎም በየሳምንቱ ፕሮግራሙን በዋና አዘጋጅነት የመምራት ኃላፊነቱን ተረክቧል።

​ውጤቱ ይፋ ከተደረገ በኋላ አስተያየቱን የሰጠው ኮሜዲያን ያሲኖ ያለፈበትን አስቸጋሪ የህይወት ጉዞ በማስታወስ ለተመልካቾች መልዕክት አስተላልፏል።

ለሰባት ዓመታት ያህል በመስተንግዶ እንዲሁም በታክሲ ረዳትነት ሲሰራ እንደነበርና የራሱ ሞባይል ስልክ እንኳን ሳይኖረው በሰው ስልክ ቪዲዮዎችን እየቀረፀ የቲክቶክ ተከታዮቹን ከአንድ ሚሊዮን በላይ ማድረስ እንደቻለ ገልጿል።

ማንኛውም ሰው በብዙ ችግርና ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ቢሆን እንኳ ህልሙን ከመከተል ወደኋላ ማለት የለበትም ያለው ያሲኖ ከምንም ተነስቶ እዚህ ትልቅ መድረክ ላይ መድረሱ ለሌሎች ተስፋ ላጡ ወጣቶች ህያው ምስክር እንደሚሆን ተናግሯል።

​ኢቢኤስ ቴሌቪዥንም የ”ቤተሰብ ጨዋታ” ዝግጅት የሚቀርብበትን ስቱዲዮ ሙሉ በሙሉ ውብ በሆነ የውስጥ ዲዛይን በማደስ ለአዲሱ ምዕራፍ ዝግጁ ማድረጉ ታውቋል።

አዲሱ አዘጋጅ ኮሜዲያን ያሲኖም የነጻነት ወርቅነህን አደራ በመረከብ ፕሮግራሙን አዝናኝና ሳቢ አድርጎ ለተመልካች ለማቅረብ መዘጋጀቱን ገልጻል።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)

#getutemesgen #getu


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1