ጋላታሳራይ ቪክቶር ኦሲሜንን ለአርሰናል አልሸጥም ሲል ማስጠንቀቂያ ሰጠ

- Advertisement -
Sidebar AD

የቱርኩ ግዙፍ ክለብ ጋላታሳራይ፣ የፊት መስመር አጥቂ ፍለጋ ላይ ለሚገኘው አርሰናል ቪክቶር ኦሲሜንን በምንም ዓይነት ሁኔታ የመሸጥ ፍላጎት እንደሌለው አስታወቀ።

መድፈኞቹ ባለፈው የውድድር ዘመን በሁሉም ውድድሮች 21 ጎሎችንቢያስቆጥርም ወጥ የሆነ አቋም ለማሳየት የተቸገረውን ቪክቶር ዮከሬስን የሚፎካከር ሌላ አጥቂ ለማስፈረም ይፈልጋሉ። በተጨማሪም ጋብሬል ሱስ ክለቡን ለመልቀቅ በመቃረቡ፣ ክለቡ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫውን ለማስከበርና በቻምፒየንስ ሊግ ስኬታማ ለመሆን የፊት መስመሩን ማጠናከር ግዴታ ሆኖበታል።

አርሰናልቀደም ሲል የዋና ኢላማው ያደረገውን አትሌቲኮ ማድሪድ አልቫሬዝን የማስፈረም እቅዱ መደናቀፉን ተከትሎ (አትሌቲኮ ማድሪድ ከሪያል ማድሪድና ባርሴሎና የቀረቡለትን ጥያቄዎች ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ)፣ ፊቱን ወደ ናይጄሪያዊው አጥቂ ኦሲሜን አዙሯል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ጋላታሳራይም በበኩሉ የአርሰናሎቹን ገብርኤል ማርቲኔሊ እና ኢታን ንዋኔሪን ለማስፈረም ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል።

ዕድሜው 27 የደረሰው ኦሲሜን ከናፖሊ ከተዛወረ ወዲህ በቱርክ በነበረው ቆይታ በ74 ጨዋታዎች 59 ጎሎችን ማስቆጠር የቻለ ሲሆን፣ በክለብ እስካሁን 175 ጎሎችን አዝንቧል።

ስለ መጪው እድሉ ተጠይቆም “በዝውውር ወቅት ወሬዎች ሁልጊዜ አሉ፤ ትኩረቴ በስራዬ ላይ ነው፣ ወደፊት የሚሆነውን አብረን እናያለን” ሲል መውጣቱን አልሸሸገም።

ነገር ግን የጋላታሳራዩ ፕሬዚዳንት ዱርሱን ኦዝቤክ ለቅርብሰዎቻቸው እንደተናገሩት “ለጋላታሳራይ ጥቅም የሌለውን ማንኛውንም ዝውውር አልቀበልም። ዋጋው ምንም ያህል ይሁን ምን ኦሲሜንን አልሸጥም” ብለዋል። ክለቡ ቀደም ሲል ከሳውዲው አል ሂላል የቀረበለትን የ130 ሚሊዮን ዩሮ (€130m) ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ይታወቃል።

ሆኖም የጋላታሳራይ አቋም ቢጠነክርም፣ የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ተጫዋቹን ለማስፈረም ቁርጠኛ እንደሆነና ኦሲሜንን ከጁሊያን አልቫሬዝ ይልቅ በቀላሉ ማግኘት የሚቻል እንደሆነ አድርጎ እንደሚመለከተው ተገልጻል።




Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: