በሳውዲ አረቢያ ህገ-ወጥ የዕፅ ዝውውር ላይ የተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን በቁጥጥር ስር ዋሉ

- Advertisement -
Sidebar AD

​#FastMereja I የሳውዲ አረቢያ የድንበር ጥበቃ ሃይል በጃዛን እና አሲር ክልሎች ባካሄዳቸው የተለያየ የቁጥጥር ኦፕሬሽኖች የድንበር ጥሰት የፈጸሙ 8 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል 124 ኪሎ ግራም ጫት እና 34 ኪሎ ግራም ሀሺሽ መያዙን አስታወቀ። የደህንነት ሃይሉ ህገ-ወጥ እፆቹ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ማክሸፉን ገልጾ፣ ከተያዙት ግለሰቦች መካከል የየመን እና የኢትዮጵያ ዜጎች እንደሚገኙበት አስታውቋል።

​በጃዛን ክልል አል-አሪዳህ ሴክተር በተካሄደ የመጀመሪያ ዙር ፍተሻ 84 ኪሎ ግራም ጫት በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ሲሞክሩ የነበሩ ስድስት የየመን ዜጎች በቁጥጥር ስር ውለዋል። በተመሳሳይ በዚህ ባለው አል-አሪዳህ ሴክተር በተካሄደ ሌላ ተጨማሪ ኦፕሬሽን 34 ኪሎ ግራም ሀሺሽ ለማስገባት የተደረገው ሙከራ በድንበር ጥበቃ አባላት በቁጥጥር ስር ውሏል።

​በሌላ በኩል በአሲር ክልል አል-ራቡአ ሴክተር በተካሄደ ተመሳሳይ የክትትል ስራ 40 ኪሎ ግራም ጫት በህገ-ወጥ መንገድ ለማስገባት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሁለት የኢትዮጵያ ዜጎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

​የሳውዲ አረቢያ የሚመለከታቸው ባለስልጣናት እንደገለጹት በቁጥጥር ስር በዋሉት ተጠራጣሪዎች እና በተያዙት እፆች ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ህጋዊ ሂደቶች የተጠናቀቁ ሲሆን፣ ሁሉም ግለሰቦች እና የተያዙት እፆች ጉዳዩ ለሚመለከተው የህግ አካል ተልከዋል።


Source: FastMereja

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1