በታይላንድ በዝናብ ወቅት ብቻ የሚከሰተው አስደናቂው የምድር “የድንጋይ ዓይን” የተፈጥሮ ክስተት ትኩረት ሳበ በሰሜን ምስራቅ ታ…

- Advertisement -
Sidebar AD
በታይላንድ በዝናብ ወቅት ብቻ የሚከሰተው አስደናቂው የምድር “የድንጋይ ዓይን” የተፈጥሮ ክስተት ትኩረት ሳበ
 
በሰሜን ምስራቅ ታይላንድ ቡኤንግ ካን ግዛት የሚገኘው እና “የምድር ዓይን” በመባል የሚታወቀው አስደናቂው የአሸዋ ድንጋይ ምድር፣ በክረምት ወቅት በሚጥለው የመንሶን የዝናብ ውኃ ሲሞላ ሙሉ በሙሉ ሰዋዊ ዓይን የሚመስል ምስል እንደሚፈጥር ተገለጸ። ይህ ተፈጥሯዊ ክስተት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በውኃ መሸርሸር ምክንያት በድንጋዩ ላይ በተፈጠረው ጥልቅ ጉድጓድ ምክንያት የሚከሰት ነው።
 
በዝናብ ወቅት ውኃው በድንጋዩ ጉድጓድ ውስጥ በሚጠራቀምበት ጊዜ፣ የጉድጓዱ ጥልቅ ማዕከል ጥቁሩን የዓይን ብሌን የሚመስል ሲሆን፤ በዙሪያው ያለው አጭር የውኃ ገጽታ ደግሞ ውጫዊውን የዓይን ክፍል ይፈጥራል። በተጨማሪም የፀሐይ ብርሃን በውኃው ላይ ሲያርፍ የሚፈጥረው ነፀብራቅ ከሰው ልጅ ዓይን ጋር ተመሳሳይነት ያለው እይታ እንዲኖረው ያደርገዋል።
 
የዝናብ ወቅት ሲያልቅ ውኃው የሚደርቅ በመሆኑ ይህ አስደናቂ ክስተት የሚታየው በክረምት ወቅት ብቻ እንደሆነ ተጠቅሷል።
 
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: