#Ethiopia | በዓለም አቀፍ አስተዳደር፣ በእኩልነት እና በሀብት ክፍፍል ዙሪያ አዳዲስና የተለዩ ፍልስፍናዊ ሀሳቦችን ያካተተው “አዲሱ የዓለም ሥርዓት” የተሰኘ መጽሐፍ በይፋ ተመረቀ።
በ340 ገጾች የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ፣ በዓለም ላይ የሕዝቦች እኩልነት፣ ፍትሕና ወንድማማችነት በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲሰፍን የዓለም አስተዳደር በአዲስ አስተሳሰብ ሊቃኝ ይገባል የሚል ጠንካራ ሞጋች ሀሳብን ያነሳል።
መጽሐፉ ይህ አስተሳሰብ በምን መልኩ ወደ ተግባር ሊለወጥ እንደሚችል ከኢኮኖሚ፣ ከመልክዓ ምድር፣ ከተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም፣ ከአካባቢ ጥበቃ፣ ከሃይማኖት፣ ከባህልና ከማህበራዊ ጉዳዮች አንጻር በስፋት ዳስሶ ያቀርባል።
በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰርፀፍሬ ስብሀት፣ እንደዚህ ያሉ አዳዲስ ሀሳቦች የምርምር አስተሳሰብን ለማሳደግና ለሀገር ግንባታ አዳዲስ አማራጮችን ለማፍራት ያላቸውን ትልቅ ሚና ገልጸዋል።
በተመሳሳይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ገዛኸኝ ፀጋው በበኩላቸው፣ መጽሐፉ በአቀራረቡ የተለየና በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊወያዩበት የሚችሉ ፍልስፍናዊ ሀሳቦችን ያካተተ መሆኑን አብራርተዋል።
ይህ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ለማድረግ ታስቦ በአማርኛ፣ በኦሮምኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ የቀረበው “አዲሱ የዓለም ሥርዓት” መጽሐፍ፣ ሀሳቡ ከኢትዮጵያ አልፎ ለዓለም አቀፍ አንባቢያን እንዲደርስ በተጨማሪ ወደ 13 ቋንቋዎች መተርጎሙም ተገልጻል።
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#NewWorldOrder Book Launch
#TadeleDriba #EthiopianLiterature
#BookLaunchEthiopia #WorldGovernment
#GlobalGovernance




Source: GetuTemesgen









No comments yet.