በአዲስ አበባ ከምትሰራበት ቤት የ7 ዓመቷን ህፃን አግታ ወደ ጎንደር በመውሰድ ከቤተሰቦቿ 3 ሚሊዮን ብር የጠየቀች የቤት ሰራተኛ በጎንደር ከተማ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለች።
የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ እንዳስታወቀው፣ መቅደስ ሞገስ የተባለችው ተጠርጣሪ ህፃኗን ካገተች በኋላ ወደ ጎንደር በመውሰድ በማራኪ ክፍለ ከተማ ዩኒቨርሲቲ አካባቢ ባለ ጫካ ውስጥ ደብቃት ነበር።
የመምሪያው አዛዥ ኮማንደር አንተነህ ቴዎድሮስ እንደገለጹት፣ ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ እና ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪዋን መያዝ ችሏል።
ተጠርጣሪዋ ከግርማ ወንድአሁን ከተባለ የአክስቷ ልጅ ጋር በመተባበር ድርጊቱን እንደፈፀመች ፖሊስ ገልጿል። ሁለቱ ለህፃኗ ቤተሰቦች በስልክ በመደወል 3 ሚሊዮን ብር የጠየቁ ሲሆን፣ ከ370 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ መቀበላቸውም ተገልጿል።
ፖሊስ በጉዳዩ የተሳተፉ ሌሎች ተጠርጣሪዎችንም ለመያዝ ክትትል እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።
addisreporter2
Source: Yeneta Tube









No comments yet.