አርሰናል እና ባየር ሙኒክ ለግማሽ ፍፃሜ ደረሱ

- Advertisement -
Sidebar AD

​የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ተጠናቀው የግማሽ ፍፃሜ ተፋላሚዎች ታውቀዋል። መድፈኞቹ እና የባቫሪያው ግዙፍ ሙኒክ ድል ቀንቷቸዋል።

​አርሰናል ወደ ግማሽ ፍፃሜ!

​ውጤት፦ አርሰናል 0 – 0 ስፖርቲንግ ሊዝበን (ድምር ውጤት፦ 1 – 0)

​በመጀመሪያው ዙር ከሜዳው ውጪ ያስመዘገበው የ 1 ለ 0 ድል አርሰናልን ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት ወደ ግማሽ ፍፃሜ አሳልፎታል። አርሰናል ለፍፃሜ ለመድረስ ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ብርቱ ፍልሚያ ያደርጋል።

​ባየር ሙኒክ ሪያል ማድሪድን አስወጣ!

​ውጤት፦ ባየር ሙኒክ 4 – 3 ሪያል ማድሪድ (ድምር ውጤት፦ 6 – 4)

​በአሊያንዝ አሬና በተደረገው አስገራሚ ጨዋታ ሃሪ ኬን፣ ፓቭሎቪች፣ ሉዊስ ዲያዝ እና ሚሼል ኦሊሴ የሙኒክን ግቦች አስቆጥረዋል።

​ሪያል ማድሪድ በአርዳ ጉለር እና ምባፔ ግቦች ቢታገሉም፣ የካማቪንጋ በቀይ ካርድ መውጣት ዋጋ አስከፍሏቸዋል። ሙኒክ በግማሽ ፍፃሜው ከፒኤስጂ ጋር ይገናኛል።

​ የግማሽ ፍፃሜ ድልድል፦

​አርሰናል 🆚 አትሌቲኮ ማድሪድ

​ባየር ሙኒክ 🆚 ፒኤስጂ

​#getu #ChampionsLeague #UCL #Arsenal #BayernMunich #RealMadrid #HarryKane #Mbappe #FootballNews #SemiFinals #ሰበርዜና #አርሰናል #ባየርሙኒክ #ሻምፒዮንስሊግ #ጌጡተመስገን #GetuTemesgen


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: