ብልጽግና ፓርቲ ቀጣይ በሚኖረው የስልጣን ዘመን ብልሹ አሰራርን በቆራጥነት እከላከላለሁ አለበ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከፍተኛ ድምጽ …

- Advertisement -
Sidebar AD
ብልጽግና ፓርቲ ቀጣይ በሚኖረው የስልጣን ዘመን ብልሹ አሰራርን በቆራጥነት እከላከላለሁ አለ
በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከፍተኛ ድምጽ ማግኘቱን ያረጋገጠው ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በቀጣይ የስልጣን ዘመኑ ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን በቆራጥነት ለመከላከል እሰራለሁ ብሏል።
ፓርቲው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያደረገውን ውጤት ተከትሎ ባወጣው መግለጫ በምርጫው ሂደት የተሳተፉ አካላትን አመስግኗል።
የህዝብ ተወካየሸች ምክር ቤት ካሉት 486 መቀመጫዎች 438ቱን ማሸነፉን ያረጋገጠው ፓርቲው በቀጣይ ሰላምንና ፀጥታን ማስፈን ላይ ሰራለሁ ብሏል።
በተለይም የኑሮ ውድነትን ለማቅለልና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ እንዲሁም በተቋማት የቢሮክራሲ ሰንሰለተን መበጠስ ላይ እንደሚያተኩር ገልጿል።
በተጨማሪም በመገባደድ ላይ የሚገኘው የሀገራዊ ምክክር ሂደት የታለመለትን ዓላማ እንዲያሳካ በሚገባ እንደሚደግፍ አስታውቋል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1