ሞተር ከአይሱዚ ጭነት መኪና ጋር ተጋጭቶ ሁለት ሰዎች ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው

- Advertisement -
Sidebar AD

#ቦንጋ | በካፋ ዞን ቢጣ ወረዳ ሸዳ ቀበሌ ውስጥ ባለሁለት እግር ሞተር ከአይሱዚ ጭነት መኪና ጋር በተፈጠረ የትራፊክ አደጋ ሁለት ሰዎች ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው።

በአደጋው የሞተር ሳይክሉ አሽከርካሪ እና ከኋላው ተሳፋሪ ሆኖ የነበረው ግለሰብ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ ለተጨማሪ ሕክምና ወደ ቦንጋ ገብረፃዲቅ ሆስፒታል መወሰዳቸውን የቢጣ ወረዳ ፖሊስ የትራፊክ አስተባባሪን ጠቅሶ የወረዳው መንግስት ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።

የአደጋው ትክክለኛ መንስኤ በትራፊክ ፖሊስ እየተጣራ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን በበኩሉ፣ ባለሁለት እግር ሞተር አሽከርካሪዎች የአደጋ መከላከያ ሄልሜት መጠቀም በአደጋ ጊዜ የጭንቅላት ጉዳትን ለመቀነስ እጅግ ወሳኝ መሆኑን በድጋሚ አሳስቧል።


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: