“ደህና ነኝ!” ሊመረቅ ነው!

- Advertisement -
Sidebar AD

የጋዜጠኛና መምህር ዐቢይ ይልማ 5ኛ “ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” የተሰኘ መንፈ-ሳይንሳዊ መፅሐፍ የፊታችን ነሐሴ 2/2018 ዓም ፣ ቅዳሜ ጠዋት 4፡00 ቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ይመረቃል፡፡

መፅሐፉ አሁን በትውልዱም ፣ በሐገራችንም የገባውን የጭንቀት ፣ የፍርሃት ፣ የባዶነት ስሜት ፣ የተስፋ መቁረጥ ፣ የካንሰር ፣ የስኳር ፣ ስትሮክና መሰል በሽታዎች ጥቃትን በዕውቀት ያክማል፡፡ በራስ ኩነኔ ፣ በሱሰኝነት ፣ በገንዘብ እጦት ወዘተ (ብቻ) ሕይወትም ኑሮም ለከበዳት ነፍስ አስገራሚ ምስጢራትን ይበታትናል፡፡ ፀሐፊው ዐቢይ ይልማ በሕይወቱ ፣ በመኖርና መሞት መካከል ከተፋለመባቸው የ12 ዓመታት የሕይወት ጦርነት አሸናፊነት ውስጥ “ደህና ነኝ ፤ እግዚአብሔር ይመስገን!” መጽሐፍ ተወልዳለች።

በምረቃው ዕለት ታላላቅ እንግዶች የሚታደሙ ሲሆን መርሀ ግብሩንም የሚያዋዙ የጥበብ መሰናዶዎችም እንደሚኖሩ ከኮሚቴው ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።


Source: FastMereja

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1