የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ ለሚገነባው አዲስ ሜጋ ኤርፖርት የሚያስፈልገውን የቢሊዮን ዶላር ብድር የማጽደቅ ሂደት ስምንት ወራት እንደሚፈጅና እስከ መጋቢት 2019 ዓ.ም ድረስ እንደሚጠናቀቅ አስታወቀ።
አየር መንገዱ የመሬት መንጥር እና የተፈናቀሉ አርሶ አደሮችን መልሶ የማቋቋም ስራዎች በከፍተኛ ሁኔታ መጠናቀቃቸውን ገልጿል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው እንደተናገሩት፣ የግንባታ ተቋራጮች ተጨማሪ ጊዜ በመጠየቃቸው የኮንትራክተሮች መረጣ ማጠናቀቂያ ጊዜ ከነሐሴ ወር ወደ መጪው ጥር መራዘሙን አስረድተዋል።
Via capital
Source: Yeneta Tube








No comments yet.