በራያ ውጥረት አለ-ነዋሪዎቹ
ከቀናት በፊት በሱዳን አዋሳኝ ሸረሪና በፌደራል ኃይሎች እና በህወሓት ታጣቂዎች መካከል የነበረው ግጭት ጋብ ቢልም፣ በራያ አላማጣ ግንባር በኩል ግን ወታደራዊ ዝግጅቱ እና ፍጥጫው ማየሉን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአላማጣ ከተማ ነዋሪ፣ የህወሓት ሠራዊት በራያ ግንባር በጨርጨር፣በቢሶበር እና ሌሎች አካባቢዎች ተሰማርተዋል ይላሉ።
«ህወሓት ሠራዊቶች ብዙ አርሚዎች በራያ ግንባር አሰማርተዋል። ለጦርነት ዝግጁ እንዲሆኑ መመሪያ ወርዶላቸዋል። ዝግጅት ያለው አሁን በጨርጨር በኩልና ቢሶበር ነው። በዛ ቡታ መርፌ አካባቢ አለ። ከዚህ በዋጃ ቆቦ፣ በጃርሮታ ጀምሮ፣ በዳንያ ለኮ፣ ሰሌን ውኃ፣ በላይ በር በባይባዋ፣ ቁሙጋ ላይ ያለውን አካባቢ ሁሉ ነው ዝግጅቱ። የዋጃን መስመር ተከተሎም የራሳቸውን አርሚ አዘጋጅተዋል።»
መካናይዝድ ጦርም በማንቀሳቀስ ቦታ እያሲያዙ ነው ብለዋል።
አሁን ባለው ወታደራዊ ዝግጅት እና እንቅስቃሴ ጦርነቱ በማንኛውም ጊዜ ሊጀምር ይችላል የሚሉት የራያ ወረዳ ነዋሪ፣ ጦርነቱ በተጀመረ ቁጥር ጉዳት የሚደርስበት የራያ ማኅበረሰብ በእጅጉ ነፃነቱን ይሻል ብለዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio
ከቀናት በፊት በሱዳን አዋሳኝ ሸረሪና በፌደራል ኃይሎች እና በህወሓት ታጣቂዎች መካከል የነበረው ግጭት ጋብ ቢልም፣ በራያ አላማጣ ግንባር በኩል ግን ወታደራዊ ዝግጅቱ እና ፍጥጫው ማየሉን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአላማጣ ከተማ ነዋሪ፣ የህወሓት ሠራዊት በራያ ግንባር በጨርጨር፣በቢሶበር እና ሌሎች አካባቢዎች ተሰማርተዋል ይላሉ።
«ህወሓት ሠራዊቶች ብዙ አርሚዎች በራያ ግንባር አሰማርተዋል። ለጦርነት ዝግጁ እንዲሆኑ መመሪያ ወርዶላቸዋል። ዝግጅት ያለው አሁን በጨርጨር በኩልና ቢሶበር ነው። በዛ ቡታ መርፌ አካባቢ አለ። ከዚህ በዋጃ ቆቦ፣ በጃርሮታ ጀምሮ፣ በዳንያ ለኮ፣ ሰሌን ውኃ፣ በላይ በር በባይባዋ፣ ቁሙጋ ላይ ያለውን አካባቢ ሁሉ ነው ዝግጅቱ። የዋጃን መስመር ተከተሎም የራሳቸውን አርሚ አዘጋጅተዋል።»
መካናይዝድ ጦርም በማንቀሳቀስ ቦታ እያሲያዙ ነው ብለዋል።
አሁን ባለው ወታደራዊ ዝግጅት እና እንቅስቃሴ ጦርነቱ በማንኛውም ጊዜ ሊጀምር ይችላል የሚሉት የራያ ወረዳ ነዋሪ፣ ጦርነቱ በተጀመረ ቁጥር ጉዳት የሚደርስበት የራያ ማኅበረሰብ በእጅጉ ነፃነቱን ይሻል ብለዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio









No comments yet.