የተኩስ አቁም ለማራዘም ከአሜሪካ ጋር ድርድር እየተካሄደ እንዳልሆነ የኢራን ባለሥልጣን ተናገሩ

- Advertisement -
Sidebar AD

በቴህራን እና ዋሽንግተን መካከል የተኩስ አቁም ለማራዘም ድርድር እየተካሄደ እንዳልሆነ የኢራን ከፍተኛ ባለሥልጣን መናገራቸውን ሮይተርስ ዘገበ።
ስማቸው ያልተጠቀሰው ከፍተኛ ባለሥልጣን “የተኩስ አቁም ለማራዘም ንግግር እየተደረገ አይደለም። ምክንያቱም አሁንም የተጀመረ ነገር ስለሌለ የሚራዘምም ነገር የለም” ብለዋል።

ከዚህ ቀደም የተደረሰውን ስምምነት አሜሪካ “በ48 ሰዓታት ውስጥ እንዳፈረሰች” እና ከቀናት በኋላ ደግሞ “ከስምምነቱ እንደወጣች” መግለጻቸውን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
የፓኪስታን የአገር ውስጥ ሚኒስትር ሞሼን ናቅቪ ወደ ቴህራን ተጉዘው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጋር ተገናኝተዋል።
ጉብኝቱን ያካሄዱት ጦርነቱን ለመግታት እና የሆርሙዝ ወሽመጥን ለማስከፈት በሚደረግ የድርድር ማዕቀፍ አማካኝነት እንደሆነ ተገልጿል።

ሰኔ ላይ አሜሪካ እና ኢራን 14 ነጥብ ያለው የመግባቢያ ስምምነት ቢፈራረሙም የተኩስ አቁሙ ተጥሷል። ስምምነቱን በመጣስም አንዳቸው ሌላቸውን ይከስሳሉ።

BBC



Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2